Daily Weather Report 26 May 29

Weather Summary for previous day

May 28, 2026

በትናንትናው ዕለት በምዕራብ ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በምስራቅ፣ በሰሜን፣ በመካከለኛዉ እና በደቡብ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ የደመና ሽፋን ነበራቸው፡፡ ከዚሁም ጋር ተያይዞ በምዕራብ ጉጂ፣ ምስራቅ ባሌ፣ አርሲ፣ ኢሉባቦር፣ ቡኖ በደሌ፣ ሆሮ ጉዱሩ፣ ቄለም፣ ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ፣ ምዕራብ፣ ምስራቅና ሰሜን ሸዋ፣ ምዕራብና ምስራቅ ሐረርጌ ፤ ሐረር፤ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብና ማዕከላዊ ጎንደር፣ ምዕራብና ምስራቅ ጎጃም፣ አዊ ዞን፣ ሰሜንና ደቡብ ወሎ፣ የኦሮሞ ብሄረሰብ ልዩ ዞን፣ ሰሜን ሸዋ እና ዋግኸምራ፣ አሶሳ፣ መተከል፣ ፋፈን፣ ጉራጌ፣ ዳውሮ፣ ስልጤ፣ ማዕከላዊ ትግራይ እና አኝዋክ ዞኖች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኙ ሲሆን፤ በአይከል 35.9 እና በዳንግላ 34.0 ሚሜ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ተመዝግቧል፡፡ በሌላ በኩል በፉኝዶ፣ በመልካ ጀብዱ፣ አዲስ ዘመን፣ ማይሀንሳ፣ መሆኒ፣ ድሬዳዋ፣ መተሐራ፣ አሸሬ፣ ጎዴ እና ቀብሪደሃር የቀኑ ከፍተኛ የሙቀት መጠን ከ35.0-40.4°C ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

On the previous day there were cloudy conditions across western, northwestern, eastern, northern, central and southern parts of our country. In addition, heavy rain was recorded in various areas: western Guji; eastern Bale; Arsi; Ilubabor; Buno Bedelle; Horo Guduru; Kelem; eastern and western Wellega; western, eastern and northern Shewa; western and eastern Harerge; Harar; western, northern, southern and central Gondar; western and eastern Gojjam; Awi zone; northern and southern Wollo; the special Oromia zone; North Shewa and Wag Hemra; Asosa; Metekel; Fafan; Gurage; Dawuro; Silte; central Tigray; and Agnuak zones, with rainfall amounts ranging from light to moderate. Very heavy rainfall was registered at Aykel with 35.9 mm and at Dangila with 34.0 mm. On the other hand, very high daytime temperatures between 35.0 and 40.4°C were recorded in Funyido, Melka Jebdu, Addis Zemen, Mayhansa, Mehoni, Dire Dawa, Metehara, Ashere, Gode, and Kebri Dehar.

Weather Forecast for next day

May 30, 2026

በነገው ዕለት በምዕራብ ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በምስራቅ፣ በሰሜን፣ በመካከለኛዉ እና በደቡብ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ የደመና ሽፋን ይኖራቸዋል፡፡ ከዚሁም ጋር ተያይዞ ከኦሮሚያ ክልል የጉጂና ምዕራብ ጉጂ፣ ቦረናና ምስራቅ ቦረና፣ ባሌና ምስራቅ ባሌ ፣አርሲና ምዕራብ አርሲ፣ ጅማ፣ ኢሉባቦር፣ ቡኖ በደሌ፣ ሆሮ ጉዱሩ፣ ቄለም፣ ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ምስራቅና ሰሜን ሸዋ፣ ምዕራብና ምስራቅ ሐረርጌ ዞኖች፤ ሐረር፤ ድሬዳዋ፤ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ባስኬቶ፣ ጌዴኦ፣ አሌ፣ ኮሬ፣ ጋርዱላ፣ ቡርጂ፣ ደቡብ ኦሞ እና ኮንሶ ዞኖች፤ በሁሉም የሲዳማ ክልል ዞኖች፤ ከሶማሌ ክልል የዳዋ፣ ሊበን፣ ኖጎብ፣ አፍዴር፣ ፋፈን፣ ቆራሄ፣ ሲቲ፣ ኤረር፣ ሸበሌ እና ጃራር ዞኖች፤ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጉራጌ፣ ምስራቅ ጉራጌ፣ ማረቆ ልዩ ዞን፣ ስልጤ፣ የም ልዩ ዞን፣ ሀድያ፣ ሀላባ፣ ከምባታ እና ጠምባሮ ዞኖች፤ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የከፋ፣ ሸካ፣ ቤንች ሸኮ፣ ኮንታ፣ ዳውሮ እና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች፤ ከጋምቤላ ክልል የአኝዋክ እና ማጃንግ ዞኖች፤ ከቤኒሸንጉል ጉሙዝ የአሶሳ፣ መተከል፣ ካማሽ እና ማኦኮሞ ዞኖች፤ ከአማራ ክልል የምዕራብ፣ ደቡብና ማዕከላዊ ጎንደር፣ ሰሜን፣ ምዕራብና ምስራቅ ጎጃም፣ አዊ ዞን፣ ሰሜንና ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ሸዋ እና ዋግኸምራ ዞኖች በብዙ ቦታዎቻቸው ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ (1-29ሚ.ሜ) መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡ በተጨማሪም በጅማ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ምዕራብ ሸዋ እና ምስራቅ ጎጃም ዞኖች ላይ በ24 ሰዓት ውስጥ ከ30 ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራል፡፡ በሌላ በኩል በጋምቤላ፣ ፉኝዶ፣ አቦቦ፣ ፓዌ፣ ሰመራ፣ ኤሊዳር ፣ በመልካ ጀብዱ፣ አዲስ ዘመን፣ ማይሀንሳ፣ መሆኒ፣ ድሬዳዋ፣ መተሐራ፣ አይሻ፣ መተማ፣ ዳሊፋጌ፣ አዋሽ አርባ፣ ጎዴ እና ቀብሪደሃር የቀኑ ከፍተኛ የሙቀት መጠን ከ35 እስከ 40 ዲግሪ ሴልሽየስ ሆኖ ይመዘገባል፡፡

Western, northwestern, eastern, northern, central, and southern parts of the country will experience cloud cover for tomorrow. In association with this, light to moderate rainfall (1–29 mm) is expected over many areas of the Guji and West Guji, Borena and East Borena, Bale and East Bale, Arsi and West Arsi, Jimma, Illubabor, Buno Bedele, Horo Guduru, Kellem, East and West Wellega, Southwest, West, East and North Shewa, and West and East Hararghe zones of Oromia Region, as well as Harari and Dire Dawa; Wolayita, Gamo, Gofa, Basketo, Gedeo, Ale, Kore, Gardula, Burji, South Omo, and Konso zones of the South Ethiopia Region; all zones of the Sidama Region; Dawa, Liben, Nogob, Afder, Fafan, Korahe, Siti, Erer, Shaballe, and Jarar zones of the Somali Region; Gurage, East Gurage, Mareko Special Zone, Silte, Yem Special Zone, Hadiya, Halaba, Kembata, and Tembaro zones of the Central Ethiopia Region; Kefa, Sheka, Bench Sheko, Konta, Dawuro, and West Omo zones of the Southwest Ethiopia Region; Agnuak and Majang zones of the Gambella Region; Assosa, Metekel, Kamashi, and Mao Komo zones of the Benishangul-Gumuz Region; West, South and Central Gondar, North, West and East Gojam, Awi Zone, North and South Wallo, North Shoa, and Waghemra zones of the Amhara Region. Furthermore, heavy rainfall exceeding 30 mm within 24 hours is expected over the Jimma, East Wellega,West Shoa, and East Gojam zones. On the other hand, daily maximum temperatures of between 35°C and 40°C are forecast for Gambella, Fugnido, Abobo, Pawe, Semera, Elidar, Melka Jebdu, Addis Zemen, Mayhansa, Mehoni, Dire Dawa, Metehara, Ayisha, Metema, Dallifage, Awash Arba, Gode, and Kebri Dehar.