Daily Weather Report 26 June22
Weather Summary for previous day
በትናንትናው ዕለት በምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛዉ እና በደቡብ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ የደመና ሽፋን ነበራቸው፡፡ ከዚሁም ጋር ተያይዞ በአሶሳ፣ መተከል፣ ሰሜን ጎንደር፣ አዊ ዞን፤ ኢሉባቦር፣ ሆሮ ጉዱሩ፣ ቄለም፣ ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ፣ ጉራጌ፣ አኝዋክ እና ማጃንግ ዞኖች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኙ ሲሆን፤ በሺንዲ 31.5ሚሜ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ተመዝግቧል፡፡ በሌላ በኩል በፉኝዶ፣ መንደር11፣ ከሚሴ፣ ድሬዳዋ፣ ጨፋ፣ ሰመራ፣ በመልካ ጀብዱ፣ ማይሀንሳ፣ መሆኒ፣ አይሻ፣ መተማ፣ አዋሽ አርባ፣ ሀራ፣ መተሐራ፣ ጎዴ እና ቀብሪደሃር የቀኑ ከፍተኛ የሙቀት መጠን ከ35.0-43.6°C ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
Yesterday, there were overcast skies across western, northwestern, central and southern areas of our country. Along with that, Asosa, Metekel, North Gondar, Awi Zone, Ilubabor, Horo Guduru, Kelem, East and West Wollega, Gurage, Agnuak and Majang zones recorded light to moderate rainfall, with heavy rainfall of 31.5 mm reported in Shindi. Meanwhile, high daytime temperatures were recorded in Funyido, Mender 11, Kemise, Dire Dawa, Cheffa, Semera, Melka Jebdu, Mayhansa, Mehoni, Aisha, Metema, Awash Arba, Hara, Metehara, Gode and Kebridahar, ranging from 35.0 to 43.6°C.
Weather Forecast for next day
በነገው ዕለት ለክረምት ዝናብ መፈጠር አመቺ የሆኑ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በምዕራብ፣ ሰሜን፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ደቡብ ምዕራብ እና መካከለኛዉ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡ ከዚሁም ጋር ተያይዞ ከኦሮሚያ ክልል የጅማ፣ ኢሉባቦር፣ ቡኖ በደሌ፣ ሆሮ ጉዱሩ፣ ቄለም፣ ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ፣ ሰሜን፣ ምስራቅ፣ ደቡብ ምዕራብና ምዕራብ ሸዋ፣ ምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ፣ አርሲና ምዕራብ አርሲ፣ ጉጂና ምዕራብ ጉጂ፣ ባሌ፣ ቦረናና ምስራቅ ቦረና ዞኖች፤ አዲስ አበባ፤ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ባስኬቶ እና ጌዴኦ ዞኖች፤ የሲዳማ ክልል ዞኖች፤ ከሶማሌ ክልል የዳዋ፣ ሊበን፣ ኖጎብ፣ አፍዴር፣ ፋፈን፣ ቆራሄ፣ ሸበሌ እና ጃራር ዞኖች፤ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጉራጌ፣ ምስራቅ ጉራጌ፣ ማረቆ ልዩ ዞን፣ ስልጤ፣ የም ልዩ ዞን፣ ሀድያ፣ ሀላባ፣ ከምባታ እና ጠምባሮ፤ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የከፋ፣ ሸካ፣ ቤንች ሸኮ፣ ኮንታ፣ ዳውሮ እና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች፤ ከጋምቤላ ክልል የአኝዋክ እና ማጃንግ ዞኖች፤ ከቤኒሸንጉል ጉሙዝ የአሶሳ፣ መተከል፣ ማኦኮሞ እና ካማሽ ዞኖች፤ ከአማራ ክልል የምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብና ማዕከላዊ ጎንደር፣ አዊ ዞን፣ ዋግኸምራ፣ ሰሜንና ደቡብ ወሎ፣ ምዕራብና ምስራቅ ጎጃም ዞኖች፣ ከትግራይ ክልል የምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ማዕከላዊና ደቡብ ምስራቅ ዞኖች በብዙ ቦታዎቻቸው ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ (1-29ሚ.ሜ) መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡ በሌላ በኩል በሰመራ፣ ኤሊዳር፣ ጋምቤላ፣ ፉኝዶ፣ አቦቦ፣ በመልካ ጀብዱ፣ ማይሀንሳ፣ መሆኒ፣ ድሬዳዋ፣ አይሻ፣ መተማ፣ ዳሊፋጌ፣ አዋሽ አርባ፣ ጨፋ፣ ጭፍራ፣ መተሐራ፣ ጎዴ እና ቀብሪደሃር የቀኑ ከፍተኛ የሙቀት መጠን ከ35 እስከ 40 ዲግሪ ሴልሽየስ ሆኖ ይመዘገባል፡፡
Tomorrow, weather conditions favorable for the formation of convective rain will persist over parts of the western, northern, northwestern, southwestern and central areas of our country. In connection with this, the following zones are expected to receive light to moderate rainfall (1–29 mm) in many places: from Oromia region Jimma, Ilubabor, Buno Bedele, Horo Guduru, Kellem, East and West Wollega, North, East, Southwest and West Shewa, East and West Hararge, Arsi and West Arsi, Guji and West Guji, Bale, Borena and East Borena zones; Addis Ababa; from the Southern Ethiopia Region Wolayita, Gamo, Gofa, Basketo and Gedeo zones; from the Sidama region its zones; from the Somali region Dawuro, Liben, Nogob, Afder, Fafan, Korahe, Shebelle and Jarar zones; from the Central Ethiopia region Gurage, East Gurage, Mareko special zone, Silt’e, the special M/ zone, Hadiya, Halaba, Kembata and Tambaro; from the Southwestern Ethiopia region Keffa, Sheka, Bench Sheko, Konta, Dawuro and West Omo zones; from Gambella region Agnuak and Majang zones; from Benishangul-Gumuz Asosa, Metekel, Mao-Komo and Kamashi zones; from Amhara region West, North, South and Central Gondar, Awi zone, Wag Hemra, North and South Wollo, West and East Gojjam zones; and from Tigray region — West, Northwest, Central and Southeast zones. Elsewhere, high daytime temperatures between 35 and 40 degrees Celsius will be recorded in places including Semera, Elidar, Gambella, Funyido, Abobo, Melka Jebdu, Mayhansa, Mehoni, Dire Dawa, Aisha, Metema, Dallifage, Awash Arba, Cheffa, Chifra, Metehara, Gode and Kebridahar.