Daily Weather Report 25 October 08
Weather Summary for previous day
በትናንትናዉ ዕለት በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የደቡብና ደቡብ ምስራቅ እንዲሁም በምዕራብ አጋማሽ የአገሪቱ አከባቢዎች የደመና ሽፋንና ክምችት ነበራቸው። ከዚሁ ጋር በተያያዘም በብዙ ቦታዎቻቸዉ ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ (1-29ሚ.ሜ) መጠን ያለዉ ዝናብ አግኝተዋል፡፡ በተጨማሪም በ በባህርዳር፣ታረኮዲ እና በቅዳሜ ገበያ በ24 ሰዓት ዉስጥ ከ30ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለዉ ዝናብ ተመዝግቧል፡፡
Yesterday, during the daytime, there were cloudy skies and drizzle in the southern and southeastern areas, as well as showers in the western highlands of the country. In many places, light to moderate rainfall (1–29 mm) was recorded. In addition, heavy rainfall exceeding 30 mm in 24 hours was recorded at Bahirdar, Tarekodi, and Kedame Gebeya.
Weather Forecast for next day
በነገው ዕለት በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት በደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገራችን አካባቢዎች እንዲሁም በምዕራብ አጋማሽ፣ በመካከለኛው፣ በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ ጠንካራ የደመና ሽፋንና ክምችት ይኖራቸዋል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ባስኬቶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋርዱላ፣ ኮሬ፣ አሌ፣ ኮንሶ፣ ቡርጅ እና ጌዲኦ ዞኖች፤ የሲዳማ ክልል ዞኖች፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የቤንች ሸኮ፣ ሸካ፣ ከፋ፣ ምዕራብ ኦሞ፣ ዳዉሮ እና ኮንታ ዞኖች፤ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጉራጌ፣ ስልጤ፣ ቀበና ልዩ ዞን፣ ምስራቅ ጉራጌ፣ ማረቆ ልዩ ዞን፣ ሀድያ፣ ሀላባ፣ የም ልዩ ዞን፣ ከምባታ እና ጠምባሮ ዞኖች፤ ከሶማሌ ክልል የሲቲ፣ ፋፈን፣ ጃራር፣ ኤረር፣ ሊበን፣ ዳዋ፣ አፍዴር፣ ሸበሌ፣ ቆራሄ እና ዶሎ ዞኖች፣ ከኦሮሚያ ክልል የጅማ፣ ኢሉባቦር፣ ቡኖ በደሌ፣ ሆሮጉድሩ፣ ቄለም፣ ምዕራብና ምስራቅ ወለጋ፣ ምዕራብ፣ ደቡብ ምዕራብና ምስራቅ ሸዋ፣ አርሲና ምዕራብ አርሲ፣ ጉጂና ምዕራብ ጉጂ፣ ምዕራብና ምስራቅ ሐረርጌ፣ ባሌ እና ምስራቅ ባሌ፣ ቦረና እና ምስራቅ ዞኖች፤ አዲስ አበባ፤ ድሬዳዋ፤ ሐረር፤ ከትግራይ ክልል የምዕራብ፣ ማዕከላዊ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ምስራቅ እና ደቡብ ምስራቅ ዞኖች፤ ከአማራ ክልል የምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብና ማዕከላዊ ጎንደር፣ ሰሜን፣ ምዕራብና ምስራቅ ጎጃም፣ አዊ ዞን፣ ሰሜንና ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ሸዋ እና ዋግኸምራ ዞኖች፤ ከአፋር ክልል የጋቢ፣ ፋንቲ፣ ቅልበቲ፣ ሀሪ እና አውሲ ዞኖች፤ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመተከል፣ ማኦኮሞ፣ አሶሳ እና ካማሽ ዞኖች፤ ከጋምቤላ ክልል የአኙዋክ፣ ኢታንግ እና ማጃንግ ዞኖች ከቀላል እስከ መካከለኛ (1-29 ሚ.ሜ) መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡ በተጨማሪም በሁራ፣ባምባሲ፣ ጉዳቱ ኮነዶሌ፣ ባቦ፣ጉሊሶ፣ ቦጂ ጮቆርሳ፣ ቤምቤ፣ ዛዪ፣ናጆ ፣ ቦጂ ቢርመጂ፣ ጋጂ፣ ዩበዶ፣ ሳዮ ኖሌ፣ኖሌ ካባ፣ ሃሩ፣ ሀሮ ሊሙ፣ሊሙ፣ጉቶ ጊዳ፣ጊዳ አያና፣ ሜዘኒጋ፣ አቤ ዶንጎሮ፣ ሳሲጋ፣ ዲጋ፣ ጎቡ ሳዮ፣ ነቀምቴ ከተማ፣ ሌቃ ዱለቻ፣ ማኮ፣ ዲጋ፣ በደሌ ዙርያ፣ ጂማ አርጆ፣ ኖኖ ኩምባ ጨዋቃ እና ሲቡ ሲሬ 24 ሰዓት ውስጥ ከ30 ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራቸዋል፡፡
Tomorrow, strong cloud cover and drizzle are expected over the southern and southeastern parts of the country that are in their second rainy season, as well as over parts of the west (Gambela), central, northeastern, and eastern regions. In addition, light to moderate rainfall (1–29 mm) is expected in these zones: From Southern Nations, Nationalities, and Peoples' Region: Wolayita, Gamo, Gofa, Basketo, South Omo, Gardula, Kore, Ale, Konso, Burji, and Gedeo zones. From Sidama Region: the zones of Sidama. From South West Ethiopia Peoples' Region: Bench Sheko, Sheka, Kefa, West Omo, Dawuro, and Konta zones. From Central Ethiopia Region: Gurage, Silte, Kebena special zone, East Gurage, Maraqo special zone, Hadiya, Halaba, Yem special zone, and the Kembata and Tambaro zones. From Somali Region: Sitti, Fafan, Jarar, Erer, Liben, Dawa, Afder, Shebelle, Korahe, and Dolo zones. From Oromia Region: Jimma, Ilubabor, Buno Bedelle, Horogudru, Kellem, West and East Wollega, West, South West and East Shewa, Arsi and West Arsi, Guji and West Guji, West and East Hararghe, Bale and East Bale, Borena and East Borena zones. Also Addis Ababa, Dire Dawa, and Harar. From Tigray Region: West, Central, Northwestern, Eastern, and Southeastern zones. From Amhara Region: West, North, South and Central Gondar; North, West and East Gojjam; Awi zone; North and South Wollo; North Shewa; and Wag Hemra zones. From Afar Region: Gabi, Fanti, Kilbati, Hari, and Awsi zones. From Benishangul-Gumuz Region: Metekel, Mao Komo, Asosa, and Kamashi zones. From Gambela Region: Agnuak, Itang, and Majang zones. Rainfall amounts are expected to range from light to moderate, between 1 and 29 mm. Additionally, in Hura, Bambasi, Gudatu Konodole, Babo, Guliso, Boji Chokorsa, Dembe, Zayi, Najo, Boji Birmiji, Gaji, Ubdo, Sayo Nole, Nole Kaba, Haru, Haro Limu, Limu, Guto Gida, Gida Ayana, Mazinga, Abe Dongoro, Sasiga, Diga, Gobu Sayo, Nekemte Town, Leka Dulecha, Mako, Diga, Bedelle Zuria, Jimma Arjo, Nono Kumba Chewaka and Sibu Sire, heavy rainfall exceeding 30 mm within 24 hours is expected.