Daily Weather Report 25 October 02
Weather Summary for previous day
በትናንትናዉ ዕለት በማዕከላዊ ትግራይ፣ ምዕራብ፣ በመካከለኛና ምስራቅ አማራ፣ ምዕራብ፣ ደቡብ፣ ምስራቅና መካከለኛ ኦሮሚያ፣ በጋምቤላ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ሲዳማ የደመና ሽፋንና ክምችት ነበራቸዉ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም በብዙ ቦታዎቻቸዉ ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ (1-29ሚ.ሜ) መጠን ያለዉ ዝናብ አግኝተዋል፡፡ በተጨማሪም በሻምቡ በ24 ሰዓት ዉስጥ ከ30ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለዉ ዝናብ ተመዝግቧል፡፡
Yesterday, there was cloud coverage and accumulation in Central Tigray, West, Central and East Amhara, West, South, East and Central Oromia, Gambella, Southwestern Ethiopia, Central Ethiopia, South Ethiopia, Sidama. In connection with this, light to moderate (1-29mm) rainfall was recorded in many places. In addition, heavy rainfall of more than 30mm was recorded in Shambu within 24 hours.
Weather Forecast for next day
በነገዉ ዕለት በሰሜን ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በደቡብ ምዕራብ፣ በመካከለኛዉ ምስራቅ እንዲሁም በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት በደቡብ እና በደቡብ ምስራቅ የሀገራችን አከባቢዎች ላይ የደመና ሽፋንና ክምችት ይኖራቸዋል፡፡ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከትግራይ ክልል የምዕራብና ሰሜን ምዕራብ ዞኖች፤ ከአማራ ክልል የሰሜን፣ ምዕራብ ደቡብና ማዕከላዊ ጎንደር፣ ሰሜን፣ ምዕራብና ምስራቅ ጎጃም፣ አዊ ዞን፤ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ፣ መተከል፣ ካማሽና ማኦኮሞ ዞኖች፤ ከኦሮሚያ ክልል ቄለም፣ ምዕራብ፣ ምስራቅና ሆሮጉድሩ ወለጋ፣ ኢሉባቦር፣ ቡኖ በደሌ፣ ጅማ፣ ምዕራብና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣ ምዕራብና ምስራቅ ሐረርጌ፣ አርሲና ምዕራብ አርሲ፣ ባሌና ምስራቅ ባሌ፤ ጉጂና ምዕራብ ጉጂ፣ ቦረናና ምስራቅ ቦረና ዞኖች፤ ሀረር፤ ድሬዳዋ፤ ከጋምቤላ ክልል የአኝዋክ፣ ኑዌር፣ ኢታንግና ማጃንግ ዞኖች፤ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የቤንች ሸኮ፣ ሸካ፣ ከፋ፣ ምዕራብ ኦሞ፣ ዳዉሮና ኮንታ ዞኖች፤ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጉራጌ፣ ምስራቅ ጉራጌ፣ ስልጤ፣ ቀበና ልዩ ዞን፣ ማረቆ ልዩ ዞን፣ ሀድያ፣ ሀላባ፣ የም ልዩ ዞን፣ ከምባታና ጠንባሮ ዞኖች፤ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወላይታ፣ ጎፋ፣ ጋሞ፣ ባስከቶ፣ ኮንሶ፣ ቡርጂ፣ጋርዱላ፣ኮሬ፣ደቡብ ኦሞና ጌዲኦ ዞኖች፤ የሲዳም ክልል ሁሉም ዞኖች፤ ከሶማሌ ክልል ፋፈን፣ ጃራርና ኤረር ዞኖች ከቀላል እስከ መካከለኛ(1-29 ሚ.ሚ) መጠን ያለዉ ዝናብ ያገኛሉ፡፡ በተጨማሪም በአሶሳ፣ ባምቢስ ማኦኮሞ ልዩ ዞን፣ ቤጊ፣ ጅማ ሆሮ፣ ጊዳም፣ ጋምቤላ፣ ሁምቦ፣ ሲራሮ፣ ሐዋሳ ዙሪያ፣ ወንዶ ገነት፣ ማልጋ፣ ቡራ፣ ቦሬ፣ አርቤጎና እና ይርጋጨፌ በ24 ሰዓት ዉስጥ ከ30 ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለዉ ዝናብ ያገኛሉ፡፡
Tomorrow, there will be cloud coverage and accumulation in the northwest, west, southwest, central, east, and the south and southeast of our country, which are the second rainy season of the Bega. In this regard, the west and northwest zones of Tigray region; the north, west, south and central Gondar, north, west and east Gojam, Awi zone of Amhara region; the Asossa, Metekel, Kemash and Mao komo zones of Benishangul Gumuz region; the Kelem, west, east and Horo Guduru Wellega, Ilubabor, Buno Bedele, Jimma, west and southwest Shewa, west and east Hararge, Arsi and west Arsi, Bale and east Bale; Guji and west Guji, Borena and east Borena zones of Oromia region, Harar; Dire Dawa; from Gambella region includes the Agniwak, Nuer, Itang and Majang zones; from the Southwestern Ethiopia region includes the Bench Sheko, Sheka, Kefa, West Omo, Dawuro and Konta zones; from the Central Ethiopia region includes the Gurage, East Gurage, Silte, Kebena Special Zone, Mareko Special Zone, Hadiya, Halaba, Yem Special Zone, Kembata and Tembaro zones; from the Southern Ethiopia region includes the Wolaita, Gofa, Gamo, Basketo, Konso, Burji, Gardula, Kore, South Omo and Gedio zones; all zones of Sidama region; and from the Somali region includes the Fafen, Jarar and Erer zones. Additionally, Asossa, Bambas, Maokomo Special Zone, Begi, Jimma Horo, Gidami, Gambella, Humbo, Siraro, Hawassa Region, Wondo Genet, Malga, Bura, Bore, Arbegona and Yirgachefe will experience heavy rainfall of more than 30 mm within 24 hours.