Daily Weather Report 25 August 31
Weather Summary for previous day
በትናንትናው ዕለት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑት የሀገራችን አከባቢዎች ላይ የደመና ሽፋንና ክምችት ነበራቸው፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም በብዙ ቦታዎቻቸው ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ (1-29 ሚ.ሜ) መጠን ያለው ዝናብ አግኝተዋል፡፡ በተጨማሪም በ ቁሉቢ፣ሀሮማያ እና ጂንካ በ24 ሰዓት ውስጥ ከ30 ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ተመዝግቧል፡፡
Yesterday, the areas of our country that benefited from winter rain experienced cloudy skies and fog. Additionally, many locations recorded rainfall ranging from light to moderate amounts (1-29 mm). Furthermore, heavy rainfall exceeding 30 mm within 24 hours was reported in Kulubi, Haromaya, and Jinka.
Weather Forecast for next day
በነገው ዕለት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑት የሀገራችን አከባቢዎች ላይ ጠንካራ የደመና ሽፋንና ክምችት ይኖራቸዋል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከትግራይ ክልል የማዕከላዊ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ደቡብ ምስራቅ፣ ደቡብ እና ምስራቅ ዞኖች፤ ከአማራ ክልል የሰሜን፣ ምዕራብ፣ ደቡብና ማዕከላዊ ጎንደር፣ ምዕራብና ምስራቅ ጎጃም፣ አዊ፣ ሰሜንና ደቡብ ወሎ፣ የኦሮሞ ብሄረሰብ ልዩ ዞን፣ ሰሜን ሸዋ እና ዋግኸምራ ዞኖች፤ ከኦሮሚያ ክልል የጅማ፣ ኢሉባቦር፣ ቡኖ በደሌ፣ ምዕራብ፣ ምስራቅ፣ ቄለምና ሆሮጉድሩ ወለጋ፣ ምዕራብ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ምስራቅና ሰሜን ሸዋ፣ አርሲ እና ምዕራብ አርሲ፣ ምዕራብና ምስራቅ ሀረርጌ ፣ ቦረና ፣ባሌ፣ ጉጂ እና ምዕራብ ጉጂ ዞኖች፤ አዲስ አበባ ፤ ሀረር፤ ከጋምቤላ ክልል የኢታንግ፣ ኑዌር፣ አኙዋክ እና ማጃንግ ዞኖች፤ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ፣ ማኦ ኮሞ፣ ካማሽ እና መተከል ዞኖች፤ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የሸካ፣ ቤንች ሸኮ፣ ከፋ፣ ኮንታ እና ዳውሮ ዞኖች፤ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የጉራጌ፣ ምስራቅ ጉራጌ፣ ቀቤና ልዩ ዞን፣ ማረቆ ልዩ ዞን ፣ የም ልዩ ዞን፣ ስልጤ፣ ሀላባ፣ ሀድያ፣ ከምባታ እና ጠምባሮ ዞኖች፤ የሲዳማ ክልል ዞኖች፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ባሰኬቶ፣ ጋርዶላ፣ ኮሬ፣ ቡርጅ እና ጌዲኦ ዞኖች፤ ከአፋር ክልል የጋቢ፣ ሀሪ እና ማሂ ዞኖች እና ከሶማሌ ክልል የሲቲ እና ፋፈን ዞኖች በብዙ ቦታዎቻቸው ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ከሚጠናከሩት የአየር ሁኔታ ክስተቶች ላይ በመነሳት በቋራ፣ጃዊ፣ቡለን፣ጉባ፣ፓዌ፣ዳንግላ፣ማንዱራ፣ጓንጓ፣ዲባጥ፣ ዌምበርማ፣ ካማሺ፣ደብረ ኤልያስ፣ባሶ ሊበን፣ኢባንቱ፣ሲቡ ሲሬ፣አሙሩ፣ደብረ ማርቆስ፣ሃሮ ቡሉክ፣ ሀሮ፣ ጉዱሩ፣ጊንዳባራት፣ጥቁር ኢንጪኒ፣ኖኖ፣ሊሙ ሳቃ፣ኢልፋታ፣ጃልዱ፣ጮቢ፣ ሜታ ሮቢ፣አዳ በርጋ፣አምቦ ዙሪያ፣ዳንዲ፣ኤጀርሳ ላፎ፣ኤጄሬ፣አቤ ዶንጎሮ፣ ሳሲጋ፣ ዲጋ፣ ጉቶ ጊዳ፣ሀሮ ሊሙ ፣ባኮ ቲቤ፣ ኢሉ ጋላነ፣ጊዳ ኣያና፣ዳኖ፣ጂባተ እና ሌቃ ዱላቻ በ24 ሰዓት ውስጥ ከ30ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡
Tomorrow, areas of our country that benefit from winter rains will experience heavy cloud cover and fog. Additionally, related to this, the following zones will receive light to moderate rainfall: from the Tigray region—Central, Northwest, Southeast, South, and East zones; from the Amhara region—North, West, South, and Central Gondar, West and East Gojjam, Awi, North and South Wollo, special zones of the Oromo ethnic group, North Shewa, and Wag Hemra zones; from Oromia region—Jimma, Ilubabor, Buno Bedele, West, East, Kellem, and Horogudru Wellega, West, Southwest, East, and North Shewa, Arsi and West Arsi, West and East Hararghe, Borena, Bale, Guji, and West Guji zones; Addis Ababa; Harar; from Gambela region—Itang, Nuer, Anoka, and Majang zones; from Benishangul Gumuz region—Assosa, Mao Komo, Kamashi, and Metekel zones; from Southwest Ethiopia region—Sheka, Bench Sheko, Kaffa, Konta, and Dawuro zones; from Central Ethiopia region—Gurage, East Gurage, Kebena special zone, Mareko special zone, Me special zone, Silte, Halaba, Hadiya, Kembata, and Tambaro zones; Sidama region zones; from South Ethiopia region—Wolayita, Gamo, Gofa, Basketo,Gardola, Kore, Burji, and Gedeo zones; from Afar region—Gabi, Hari, and Mahi zones; and from Somali region—City and Fafen zones. These areas will receive rainfall ranging from light to moderate amounts in many locations. Furthermore, due to ongoing weather disturbances, the following areas are expected to receive heavy rainfall exceeding 30 millimeters within 24 hours: Quara, Jawi, Bullen, Guba, Pawe,Dangila, Mandura, Guangua, Dibate, Wemberma, Kamashi, Debre Elias, Baso Liben, Ibantu, Sibu Sire, Amuru, Debre Markos, Haro BuluK, Haro, Guduru, Gindabarat,Tikur Inchini, Nano,Limu Seka, Ilfata, Jaldu, Cobi, Meta Robi, Ada Berga, Ambo Zuria, Dandi, Ejersa Lafo, Ejere,Abe Dongoro, Sasiga, Diga, Guto Gida, Haro Limu, Bako Tibe, Ilu Galan, Gida Ayana, Dano, Jibat, and Leka Dulacha zones.