በሚቀጥሉት ቀናቶች ከሚኖሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ላይ በመነሳት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አከባቢዎች ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ብዙ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ (ከ1-29 ሚ.ሜ) መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡ በተጨማሪም አልፎ አልፎ በውሃ አካላትና በከባቢ አየር ውስጥ ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ላይ በመነሳት በጥቂት የደቡብ፣ ደቡብ ምዕራብ እና ምዕራብ የሀገሪቱ አከባቢዎች ላይ በ24 ሠዓት ውስጥ ከ30 ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡