21-30_April 2024
በመጪዎቹ የኤፕሪል ሶስተኛዉ አሥር ቀናት ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በአብዛኛዎቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የሀገሪቱ አካባቢዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉና በተለይም የምድር ወገብን አርጦ ወደ ሀገራችን የሚገባው ዕርጥበት አዘል የአየር ሁኔታ ጋር ተያይዞ የተሻለ የደመናና የዝናብ ሥርጭት በደቡባዊው አጋማሽ፤ በመካከለኛው እና በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ቀጣይነት እንደሚኖራቸዉ የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡