1-10 September 2025

Bulletin

በመጪዎቹ የሴፕቴምበር የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎች ላይ በተለይም በምዕራብ አጋማሽ እንዲሁም በመካከለኛው የሀገሪቱ አከባቢዎች ላይ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ መካካለኛው፣ እንዲሁም በምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚኖራቸው አሀዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመላክታሉ ፡፡