1-10 January 2026

Bulletin

በሚቀጥሉት የጃንዋሪ የመጀመሪያው አሥር ቀን ዝናብ ሰጭ የአየር ሁኔታ ክስተቶች በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የደቡብ እና የደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አከባቢዎች በተለይም በመጀመሪያዎቹ ቀናቶች ላይ የተሻለ ገጽታ ይኖራቸዋል፡፡ በመሆኑም የደቡብ ኦሮሚያ፤ ሲዳማ ክልል፤ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡባዊ እና የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ዞኖች ላይ አነስተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ ፡፡ በመሆኑም በደቡብ ኦሮሚያ የሚገኙ የቦረና፣ ምስራቅ ቦረና፣ ምዕራብ ጉጂ እና ጉጂ ዞኖች፤ እንዲሁም የዳዋ እና ሊበን ዞኖች ላይ የሚገኘዉን አነስተኛ መጥን ያለዉ ዝናብ በአግባቡ በመሰብሰብ ሊኖር የሚችለውን አሉታዊ ተጽዕኖ መቀነስ ያስፈልጋል ፡፡