
በመጪው ወር ለዝናብ መፈጠር አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በአብዛኛዎቹ የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ እንደሚጠናከሩና ከዚህም ጋር ተያይዞ ከቀደሙት ሶስት የበልግ ወራት በመጠንም ሆነ በሥርጭት የተሻለ ዝናብ በብዙ የሀገሪቱ ቦታዎች ላይ ሊኖር እንደሚችል የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ ከቀላል እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ በአብዛኛው የሀገሪቱ አካባቢ ላይ እንደሚኖርና በአንዳንድ ሥፍራዎችም ላይ ከባድ ዝናብ የሚዘወተርና አልፎ አልፎ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል እንደሚችል ይጠበቃል።