በመጪው የዲሴምበር ወር በአብዛኛዎቹ የሀገሪቱ አከባቢዎች ላይ ከሳይቤሪያ ከፍተኛ የአየር ግፊት ላይ በመነሳት ወደ ሀገራችን የሚነፍሰው ደረቅ እና ቀዝቃዛ አየር ቀጣይነት እንደሚኖረው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም የበጋው ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ የአየር ሁኔታ በአብዛኛዎቹ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሚስተዋል ሲሆን፤ የሌሊትና የማለዳዉ ቅዝቃዜ በተለይም በሰሜን፣ ምስራቅ፣ መከከለኛዉና ደቡብ ደጋማ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሌሊቱና የማለዳው ቅዝቃዜ አልፎ አልፎ ሊጠናከር እንደሚችል ይጠበቃል፡፡