
በመጪው የጁን ወር ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በተለያዩ የሀገሪቱ ሥፍራዎች ላይ አንጻራዊ ጥንካሬ እንደሚኖራቸው አሀዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም በተለይም በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛዉና በምስራቅ የሀገሪቱ አከባቢዎች ላይ ዝናቡ በመጠንም ሆነ በሥርጭት የተሻለ እንደሚሆን የሚጠበቅ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎችም ላይ አልፎ አልፎ ከሚጠናከሩ ደመናዎች ላይ በመነሳት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለዉ ዝናብ ይኖራቸዋል ፡፡