Midseason of kiremt 2024 outlook

Bulletin

በሚቀጥሉት የኦገስትና የሴፕቴምበር ወራት ከአትላንቲክና ከህንድ ውቅያኖስ የሚገባው እርጥበት አዘል የአየር ሁኔታ በተለይም በሰሜንና በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ በመጠንም ሆነ በሥርጭት የተሻለ ሆኖ ሊቀጥል እንደሚችል ከመጠበቁም በላይ በኦገስት ወር በአንዳንድ ቦታዎች ላይ በፀሐይ ሀይል ተጠናክረው ከሚፈጠሩ የደመና ክምችቶች በረዶ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ አልፎ አልፎ ይኖራል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በሴፕቴምበር ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ክስተቶች የፀሀይን አቅጣጫ ተከትለው ወደ ደቡብ ማፈግፈግ ስለሚጀምሩ በደቡብ ምዕራብና በደቡብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የበጋው ዝናብ ቀስ በቀስ መጣል ይጀምራል፡፡