የካሜሮን ልኡክ በኢንስቲትዩቱ

15 Aug, 2024 News

photo_2024-08-15_07-01-56

ከካሜሩን ከሚቲዎሮሎጂ ከግብርና እና ከአካባቢ ጥበቃ ሚኒስቴር የተውጣጡ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ውስጥ በመገኘት የስራ ጉብኝትና የልምድ ልውውጥ እያደረጉ ነው። ስምንት አባላት ያሉት ይህ ልኡክን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተርና በዓለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፕሬዝዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ በመቀበል የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክታቸውን ካስተላለፉ በኋላ በኢትዮጵያ ጥሩ ቆይታ እንዲኖራቸው ተመኝተዋል ቡድኑ ከነሐሴ 6 እሰከ 11 ቀን 2016 ዓ.ም በኢንስቲትዩቱ የሚከናወኑትን ስራዎች በመከታተል የልምድ ልውውጥ ያደርጋሉ ።