የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ከመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ከመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ጋር የቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ምዕራፍ ሁለትን በቅንጅት ለመተግበር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡
ነሃሴ 11 ቀን 2016 ዓ.ም የተፈረመው ይህ ስምምነት በቆላማ አካባቢ ያለውን ዕምቅ አቅም እና ሃብት በመጠቀም የተሻለ ውጤት ለማምጣት በሚደረገው ስራ ውስጥ ኢንስቲትዩቱ ድርሻውን በሙሉ አቅሙ እንደሚወጣ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተርና በአለም የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፕሬዝዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ ገልፀዋል።