News

በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የደቡብና ደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች ላይ መደበኛ እና ከመደበኛ በታች ዝናብ እንደሚኖራቸው ተጠቆመ

photo_2025-01-23_14-41-51

photo_2025-01-23_14-42-12

የበጋ 2017 ወቅት በትሮፒካል ፓስፊክ ውቅያኖስ የባህር ወለል ሙቀት ከመደበኛ በታች መቀዝቀዝ (ENSO-LA NINA) ሲሆን እንዲሁም የሰሜናዊ ህንድ ውቅያኖስ የባህር ወለል ሙቀት ከመደበኛ ጋር የተቀራረበ (IOD- NEUTRAL) ሆኖ ሊቆይ እንደሚችል የተተነበየ ሲሆን ከዚሁ ጋር

በተያያዘ የወቅቱ ዝናብ አጀማመር በደቡብ አጋማሽ አካባቢዎች ላይ መደበኛ ፈሩን ተከትሎ የሚጀምር ሲሆን በአወጣጥ ረገድ ግን ቀድሞ ሊወጣ እንደሚችል ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

የኢንስቲትዩቱ የበጋ ወቅት ትንበያን ይፋ ባደረገበት በዚህ መድረክ በአጠቃላይ በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት የቦረናና ጉጂ ዞኖች፤ ሲዳማ እና ደቡብ ኢትዮጵያ መደበኛ ዝናብ የሚኖራቸው ሲሆን፤ የሶማሌ ክልል ደቡባዊ ክፍል ደግሞ ከመደበኛ በታች የሆነ የዝናብ መጠንና ስርጭት እንደሚያገኙ በትንበያው የተመላከተ ሲሆን የሚመለከታቸው አካላትና ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ ማደረግ እንደሚገባው ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል።

Article info

30 Aug, 2024
News