21-31_May_2023 |
|||||
በሜይ የሁለተኛ አስር ቀናት የበልግ ዝናብ ሰጪ የአየር ሁኔታ ገጽታዎች አንፃራዊ በሆነ መልኩ በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ተጠናክሮ ተስተውሏ፡፡ በተጨማሪም የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገሪቱ አከባቢዎች ላይ በመጠንም ሆነ በስርጭት ረገድ አነስተኛ የዝናብ ስርጭት ነበራቸው በሚቀጥለው የሜይ የመጨረሻዎቹ አሥራ አንድ ቀናት ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በምዕራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ይጠናከራሉ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም በመጠንም ሆነ በሥርጭት የተስፋፋ ዝናብ የሚኖር ሲሆን እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች እንደሚጠናከር የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ። Back to List |
|||||